የኢትዮጵያዉን ሠራተኞች እሮሮ በሳዑዲ

በኮንትራት ሠራተኝነት ወደአረብ ሀገሮች የሚሄዱ ኢትዮጵያዉያን የሚደርስባቸዉ በደል ከጊዜ ወደጊዜ መባባሱ ይሰማል። በቅርቡ ስዑዲ አረቢያ ዉስጥ ህይወታቸዉን ያጡና የአካል ጉዳት የደረሰባቸዉ እህቶች ጉዳይ የችግሩን አስከፊነት ያመለክታል።