የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ ቃለ ምልልስ ሲዳሰስ

 በእስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

 

    «ገራገር ይመስላል» አለኝ አንድ ወዳጄ ትክ ብሎ ምስላቸውን በመመልከት። «ውዥምዥም ሳይሆን አይቀርም» ብሎ ምስሉ ያረፈበትን የአውራአምባ ጋዜጣ ሲያቀብለኝ ከት ብዬ ሳቅኹኝ። የአማርኛ ችሎታው ላቅ ያለ ነው። የእኔ አላዋቂነት መቀለጃው ነው።