የኤርፖርቶች ድርጅት ሥራ አስፈጻሚን ጨምሮ አራት ሰዎች በሙስና ተጠርጥረው ተከሰሱ

–    ሥራ አስፈጻሚው ከአገር ውጭ በመሆናቸው ፍርድ ቤት አልቀረቡም

በታምሩ ጽጌ

የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ዓለሙን ጨምሮ፣ ሦስት ኃላፊዎችና አንድ ነጋዴ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ትናንትና ክስ ተመሠረተባቸው፡፡