ንግድ ባንክ ለ40/60 ቤቶች ፕሮጀክት 1.12 ቢሊዮን ብር ብድር ፈቀደ

–    ባንኩ ምን ያህል ገንዘብ ለሚቆጥቡ ቅድሚያ እንደሚሰጥ አልወሰነም

በውድነህ ዘነበ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአዲስ አበባ አስተዳደር ሊገነባ ላቀደው የ40/60 ቤቶች ፕሮጀክት 1.12 ቢሊዮን ብር ብድር ፈቀደ፡፡ አስተዳደሩ ለሚበደረው ብድር የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ዋስትና ሰጥቷል፡፡