ኢትዮጵያውያንና ዓለም አቀፍ ምሁራን የግራዚያኒ ሐውልት እንዲፈርስ ጥያቄ አቀረቡ

በሔኖክ ያሬድ

ባለፈው ወር በድሬዳዋ ከተማ በተካሄደው 18ኛው የኢትዮጵያ ጥናት ዓለም አቀፍ ጉባዔ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አገር ምሁራን፣ በኢጣሊያ አፊሌ ከተማ የተገነባው የፋሺስት ጦር ወንጀለኛው ሩዶልፍ ግራዚያኒ ሐውልት እንዲፈርስ ወይም እንዲለወጥ የኢጣሊያ መንግሥትን ጠየቁ፡፡