የእስራኤል እና የፍሊስጤም ግጭት

የእስራኤልና የፍሊስጤም ሚሊሻዎች በሮኬትና በቦምብ ጥቃት ከጀመሩ ዛሬ ስድስተኛው ቀን ነው። የእስራኤል ጥቃት ከጀመረበት ካሳለፍነው ረቡዕ ወዲህ ትናንት ለጋዛ እጅግ አሳዛኝ ቀን ነበር። በጋዛ ከተማ ቤቶች ላይ ያነጣጠረ የእስራኤል የአየር ጥቃት ቢያንስ 11 ሰላማዊ ሰዎችን ሲገድል 30 የሚሆኑትን አቅስሏል።