የእብዶቹ መንግስትና ሕገ-መንግስታቸው
ሉሉ ከበደ (ጋዜጠኛና ደራሲ)
ያለፈው የወያኔ መሪ ባለቤት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ትግራይን የኢንዱስትሪ ማእከል ለማድረግ መለስ ዜናዊ አቅዶት የነበረውን፤ ጽፎ ጽፎ ያስቀመጠውን ህልሙን ተግባር ላይ ለማዋል መንቀሳቀስ እንደምትጀምር በቅርቡ በይፋ አውጃለች። ይህ ሰው የኢትዮጵያ መሪ ይባል የነበረ ነው። ለምንድነው ከኢትዮጵያ ህዝብ ደብቆ ለትግራይ ብቻ ያን ሁሉ ራዕይ አልሞ፤ አቅዶ፤ ነድፎ እንዲፈጸም አደራ ብሎ የነበረው? ለሚለው ጥያቄ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የራሱን መልስ ይስጥ።ወይዘሮዋ ይህንን ተልኮ የምትፈጽመው ኢፈርት የሚባለውን የንግድ ድርጅት በመምራት ነው።