ማን ጸሎት ያሳርግ

በ ለምለም ፀጋው

ወይ ነውር አይገዛው

አምልኮት ዓልነካው፤

የኢትዮጵያን ሰው ሁሉ

በቃሊቲ አጎረው።

ይድነቃችሁ ብሎ

በየሱስ ስም ማለ፤

የመለስን ወንጌል

እንደ ክታብ አርጎ

በአንገቱ ሰቀለ።

        ለሁሉም ለመሆን

        አዲሱ ምንስቴር በቃሊቲ ሳይቀር፤

        አርብ ሰኞ ሳይል

        አለ ዓላህ አክብር።

ምነው የኔ ወዳጅ

ጓዴ የጴንጤ አማኝ                                    

አያቴ ኦርቶዶክስ

የሚያምኑ በየሱስ

የዓባቴ ወገኖች

አሉ ብዙ እስላሞች

በክርስትና መልክ እስኪ ልጠይቅህ

በቃሊቲ ቦታ ቁርስ ምሳ ሲቀርብ

ማን  ጸሎት ያሳርግ

ብለህ ታውጃለህ

ዳዊትን ይደገም

ወይስ ቁርሃን ያቅራ

በዱር በገደሉ ለመብቱ ሲያቅራራ።

           ዐረ ባላህ በሉ ወይንም በየሱስ

        እስከመቸ ድረስ

        እንዲህ እንታመስ

አዳምጠኝ ይልቅስ ወሪውን ልንገርህ

ብቻውን አልቅሷል ዖሮሞው አባትህ

ለአማራዋ እናትህ

ተው እንጅ ዓትቀልድ ምነው ምኑ ነካህ

ከለቅሶው ያልደረስህ

አሁን ገና ገባኝ አላህን ፈርቶ ነው

ሰላም በማወጅህ

        ዐረ ባላህ በሉ ወይንም በየሱስ

        እስከመቸ ድረስ

        እንዲህ እንታመስ

 

© ለምለም  ጸጋው በስልምና ሃይማኖትም ሆነ መብታቸውን ለማስጠበቅ በመናገራቸው በእስር ቤት ለሚማቅቁ ሁሉ

(http://www.ethiomedia.com/assert/4785.html)

(http://www.youtube.com/watch?feature=endscreen&v=t6Agm1q_YpM&NR=1)

http://www.youtube.com/watch?feature=endscreen&NR=1&v=tOFOCAtXzx8