የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ 2000 አውቶብሶች እንደሚያስፈልጉ ተገለጸ
ኅብረተሰቡ በከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት እየተንገላታ ነው
በታምሩ ጽጌ
ከንጉሡ ዘመን ጀምሮ የነዋሪዎችና የትራንስፖርት አቅርቦቱ ተጣጥሞ እንደማያውቅ የሚነገርላት የአዲስ አበባ ከተማ፣ በተለይ በአሁኑ ጊዜ የከተማዋን መስፋትና የነዋሪዎችን ብዛት ተከትሎ የተከሰተውን እጥረት ለመፍታት 2000 አውቶብሶች እንደሚያስፈልጉት፣ የአዲስ አበባ መንገድና ትራንስፖርት ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡