በአጋጣሚ የተገናኙት ሚኒስትሮች በዋጋ ግሽበት ጉዳይ ተጠመዱ

በምስሉ ከግራ ወደ ቀኝ የሚታዩት አቶ ዓሊ ሲራጅ (የንግድ ሚኒስትር ዴኤታ)፣ አቶ ተፈራ ደርበው (የግብርና ሚኒስትር) እና አቶ ጌታቸው መንግሥቴ (የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ) ሲሆኑ፣ በገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ የመተካካት ፖሊሲ መሠረት ወደ መንግሥት ኃላፊነት ከመጡ ወጣት መሪዎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡