የሶሪያ ዉጊያ፤ተቃዋሚዎችና ሐያሉ ዓለም

ምዕራባዉያኑ የኮሎኔል ሙዓመር ቃዛፊ አገዛዝን ለማስገድ ያዘመቱትን አይነት ጦር በፕሬዝዳት በሽር አል-አሰድ ላይ ለማዝመት እስካሁን አቅሙና ፍላጎቱ ያላቸዉ አይመስልም።ቢኖራቸዉ እንኳን የሩሲያና የቻይና ተቃዋሚዎቻቸዉን እንደከዚሕ ቀደሙ ማግባባት ወይም ማታለል አልቻሉም።