ከአሥር ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከኢትዮጵያ 15 ቢሊዮን ዶላር መውጣቱ ተረጋገጠ

•    ካቻምና ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ታጥቷል

በአስራት ሥዩም

እ.ኤ.አ. ከ2001 እስከ 2010 ባለው ጊዜ ውስጥ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ሕጋዊ በሆነና ባልሆነ መንገድ ከኢትዮጵያ እንዲወጣ ተደርጎ ወደ ውጭ ገበያዎች ማምራቱን በቅርቡ ይፋ የሆነ ሪፖርት አመለከተ፡፡