‹‹መድረክ ውስጥ የኢሕአዴግን የሥልጣን ፍርፋሪ የሚፈልግ ማንም የለም››
አቶ ግርማ ሰይፉ፣ የመድረክ ብቸኛው የፓርላማ ተወካይ
ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በመሆን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን የተቀላቀሉት የመድረክ አመራር አባል አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥትን አቋም ለገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መድረክንና ኢሕአዴግን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበው ነበር፡፡