አፍሪቃ እና አንደኛ የጋዳፊ ሙት ዓመት

ኮሎኔል ሙአመር ኧል ጋዳፊ ከተገደሉ እነሆ ዛሬ አንድ አመት ሆናቸው። እኝህ ሰው ላለፉት 41 ዓመታት በአገራቸው ሊቢያ ብቻ ሳይሆን በብዙ የአፍሪቃም መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ፣እንዲሁም፣ በፖለቲካው ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።