የአሜሪካን ምርጫ ዘመቻ 2ኛ ክርክር

ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ የምርጫ ቅስቀሳና ፉክክሩ ቀጥሏል። ትናንት ኒውዮርክ በተካሄደዉ ሁለተኛ የምርጫ ፉክክር ክርክር ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ባለፈዉ ከገጠማቸዉ ሽንፈት አገግመዉ ታይተዋል። በተለይም በሀገር ዉስጥ ኤኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ተፎካካሪያቸዉን ሚት ሮምኒን መብለጣቸዉ ተገልጿል። ፕሬዝደንታዊ የምርጫ ክርክሩ ሶስተኛ ዙር ይቀረዋል።