የበአሉ ግርማ ጆሮጠቢ
ተስፋዬ ገብረአብ
በኛ ዘመን የብእር ሰው ሆኖ መፈጠር መረገም ሆኖ ይሰማኛል። ከቡቃያው የሚነጋገር፣ በሁዳዱ ላይ ሽምጥ ፈረስ የሚጋልብ፣ ውሎው ከዋልካው፣ ማምሻው ከመልካው የሆነ ገበሬ እንዴት እድለኛ ነው? የኛ ዘመን ብእረኛ ህይወቱ በሰላዮች የተከበበ ነው። ተፈጥሮው ነውና አለመፃፍ አይችልም። መፃፍ ደግሞ አደጋ ነው። በአሉ ግርማ እንዲህ ባለ ችግር ውስጥ አልፎ፣ በከንቱ ያለፈ ደራሲ ነበር። ደርግ ብዙ ሰላዮች መድቦበት ነበር።