ሕልሜ ቅዠት ባይሆን..

ይድረስ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ

ሉሉ ከበደ (ጋዜጠኛና ደራሲ)

ከሀያ አንድ ዓመታት የሸፍጥ፤የውሸት፤የተንኮል እና የጭካኔ አገዛዙ በሗላ በኢትዮጵያ ህዝብ እንቢ ባይነትና በሟቹ አንባገነን “እኛ እንጂ የሚገዛችሁ የለም” የተግባርና የስነልቡና ጦርነት፤በአሜሪካኖች፤ በእንግሊዞች ወይም ደሞ በኔቶ ያየር ድጋፍ ሳይሆን በእግዚአብሄር ጣልቃ ገብነት፤መለስ ዜናዊ የፈጀውን ፈጅቶ ገና ሳይበቃው፤ ያን ሁሉ በህዝብ ላይ የተሸከመውን ንቀት፤ ያን ሁሉ በአማራ ላይ ያረገዘውን ጥላቻ፤ ያን ሁሉ ለዛ የሌለው ንግግር እንደተጫነ፤ የልቡን እስከመጨረሻው ሳያደርስ ኢትዮጵያን ሳይበትንና የትግራይን መንግስት በይፋ ሳያውጅ እንደወጣ በዚያው ቀረ። የእግዚአብሄር ፍርድ ይግባኝ የለውም። እሱ የፈረደባቸው የእስር ግዜያቸውን ሳይጨርሱ፤ ሞት የፈረደባቸውም ተራቸውን በመጠበቅ ላይ እንዳሉ፤ ለምን እንደቀደማቸው የሚታወቅ ነገር የለም።ቀደማቸው።ይገርማል።