ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ውስጥ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ህልፈት ምክንያት የተደረገው የስልጣን ሽግግር በአንድ ድርጅት ውስጥ ቢሆንም ጥሩ መሰረት እንደተጣለ ተገለጸ። በአሁኑ ወቅት በኢህአደግ ውስጥ ህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይም ሆነ ሌላ አካል የበላይነት ቦታ ይይዛል የሚል እምነት እንደሌለም ተጠቅሷል።