መፍትሄ ያላገኘው በሊቢያ የሚገኙ ስደተኞች ጉዳይ

በመቶዎች የሚቆጠሩ ተገን ጠያቂዎች በሊቢያ ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው እንደሆነ አንዳንድ ስልክ ደውለው የገለፁልን ኢትዮጵያውያን አስታወቁ። «ስለኛ ተጠያቂ አካል የሆነ መፍትሄ እንዲፈልግልን እና እንዲያነጋግረን» ጠይቁልን ሲሉም ለዶይቸቬለ ጥሪ አቅርበዋል።