የአንጌላ ሜርክል የአተንስ ጉብኝት

የጀርመን መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ዛሬ በግሪክ መዲና አተንስ ባደረጉት ጉብኝት ከሀገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትር አንቶኒስዮስ ሳማራስ ጋ ተወያዩ። ሜርክል በዚሁ ስድስት ሰዓት በቆየው ጉብኝታቸው የፊናንስ ቀውስ የገጠማት ግሪክ የጀመረችውን የተሀድሶ ሂደት አሞግሰዋል።