የመስቀል በዓል አከባብር-በጀርመን

በኢትዮጳያ ዉሃን ጠጥቶ፤ እሸትዋን በልቶ፤ ያደገ ዜጋ ሁሉ፤ ምን ከአገር ርቆ ቢሄድ፤ ያደገበትን ባህሉን ይረሳል ማለት ዘበት ነዉ። በዉጭ አገር ሲኖር፤ ዘመን መለወጫ እንዲሁም የተለያዩ የመንፈሳዊ በዓላት፤ በኢትዮጳያ በሚከበርበት ቀንም ባይሆን፤ እንደ አመችነቱ ታይቶ፤ በአዲሱ አገር ያፈራዉን ወዳጅ ጎረቤት ይዞ፤ ማክበሩ፤ አይቀሪ ነዉ።