ንግድ ባንክ ያለመያዣ ብድር መስጠት እንደሚቻል አስታወቀ

–    በቂ የውጭ ምንዛሪ አለኝ ቢልም ኤልሲ መክፈት አልተቻለም
–    ከሙስና ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን መግለጽ አልደፈረም

በታምሩ ጽጌ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአንድ ደንበኛ ወይም ድርጅት ብድር ለመስጠት መያዣ (ኮላተራል) አማራጭ አለመሆኑንና ደንበኛውንና ቢዝነሱን በማወቅ ብቻ ማበደር እንደሚቻል አስታወቀ፡፡