በሰሜን አፍሪቃ የተጀመረው የዴሞክራሲ ለውጥንና ጥቁሩ አፍሪቃ

አቶ ግርማ ሞገስ በሙያ ሲቪል ኢንጂነር ናቸው። በዚህ ሙያ ከሃያ ዓመታት ለሚበልጥ ጊዜ በካናዳና  ዩናይትድ ስቴትስ አገልግለዋል።

ከ97 ቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ወዲህ ግን የኢትዮጵያን የሥልጣን ሽግግር ታሪክ መመርመር እንደጀመሩና በቅርቡም በርእሱ ላይ መጽሐፍ እንደሚያሳትሙ ገልጸውልናል። አቶ ግርማ ሞገስ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ላይ አያሌ ጽሁፎችን አስነብበዋል።  እነዚህን መሠረት በማድረግ ነው ትዝታ በላቸው ለቃለ ምልልስ የጋበዘቻቸው፤ ሙሉውን ውይይት እንዲያዳምጡ እንጋብዛለን።