የሁለቱ ሱዳኖች ስምምነት

ሁለቱ ወገኖች ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በተፈራረሙት ስምምነት መሰረት የተቋረጠው ወሳኙ የነዳጅ ዘይት ምርትና ሽያጭ ይቀጥላል ። የደረሱበት ስምምነት ደቡብ ሱዳን በሱዳኑ የቀይ ባህር ወደብ በኩል ነዳጅ ዘይት ለውጭ ገበያ ማቅረብ ያስችላታል ።