በኢትዮጵያ ታስረው የነበሩት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞች ተፈቱ

በድምሩ 1900 እስረኞች አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከእስር ይፈታሉ

ጋዜጠኞች ዮሐን ፐርሾን (በግራ) እና ማርቲን ሺቢ (በቀኝ) Johan Persson (L) and Martin Schibbye (R)Ethiopia Zare (ሰኞ ጳጉሜን 5 ቀን 2004 ዓ.ም. September 10, 2012)፦ ላለፉት አስራ አራት ወራት በእስር የቆዩትና በሽብረተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው የ11 ዓመት እስራት የተፈረደባቸው ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ማርቲን ሺቢ እና ዮሐን ፐርሾን ዛሬ ጳጉሜን 5 ቀን ማምሻውን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከ11 ሰዓት በኋላ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ። ከቃሊቲ ወጥተው በቀጥታ ወደ ስዊድን ኤምባሲ መሄዳቸው ታውቋል።