በኢትዮጵያ ታስረው የነበሩት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞች ተፈቱ
በድምሩ 1900 እስረኞች አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከእስር ይፈታሉ
Ethiopia Zare (ሰኞ ጳጉሜን 5 ቀን 2004 ዓ.ም. September 10, 2012)፦ ላለፉት አስራ አራት ወራት በእስር የቆዩትና በሽብረተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው የ11 ዓመት እስራት የተፈረደባቸው ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ማርቲን ሺቢ እና ዮሐን ፐርሾን ዛሬ ጳጉሜን 5 ቀን ማምሻውን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከ11 ሰዓት በኋላ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ። ከቃሊቲ ወጥተው በቀጥታ ወደ ስዊድን ኤምባሲ መሄዳቸው ታውቋል።