ጋዜጠኞችና የፖለቲካ መሪዎች አልተፈቱም (VOA)

የኢትዮጵያ መንግሥት አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ፥ ሁለቱን ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ጨምሮ 1,923 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑን የፍትሕ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ አስታውቀዋል። በሽብርተኝነት ተከሰው የታሠሩ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ጉዳይ ግን ለይቅርታ ቦርዱ አለመቅረቡን ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የእስክንድር ፍሬው ዘገባ ያዳምጡ፡፡