የአዳማ ነዋሪዎች በውኃ ጥም እየተቃጠሉ መሆናቸውን ተናገሩ

በታምሩ ጽጌ

ከቆቃ ወደ አዳማ (ናዝሬት) የተዘረጋው የውኃ መስመር በጐርፍ በመወሰዱ ላለፉት 15 ቀናት የአዳማ ነዋሪዎች በውኃ ጥም እየተቃጠሉ መሆኑን አስታወቁ፡፡