በጎ ምክር ለጓዶች
ተስፋዬ ገብረአብ
የኢህአዴግ የስልጣን ሽኩቻ ተባብሶ በመቀጠሉ የአመራር አባላቱ ዝግ ስብሰባ ላይ ስለመሆናቸው እየተሰማ ነው። ይህን ሽኩቻ ከህዝብ ጆሮ ለመሰወር ሲባል ስለ ኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በቴሌቪዥን የተላለፈው ቀሽም ድራማ ነበር። የአመራር አባላቱ እጃቸውን እያወጡ ድምፅ ሲሰጡ በቲቪ ይታያል። በምን ጉዳይ ላይ ነው ተከራክረው በድምፅ ወሰኑት? አልተገለፀም። ከኢህአዴግ ነባር ልምድ አንፃር፣ ከስብሰባው በፊት ጋዜጠኞች ገብተው ምስል ቀርፀው እንዲወጡ እንደሚደረግ አውቃለሁ። ከዚያም በሮችና መስኮቶች ተዘግተው ስብሰባው ይቀጥላል።