‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ለቅንጅት ሰዎች የተወሰኑ የሚኒስትርነት ቦታዎችን ለመስጠት ቃል ገብተውልን ነበር››

ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ፣ የአገር ሽማግሌዎች ኅብረት ሊቀመንበር

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዜና ዕረፍት ከተነገረበት ከነሐሴ 14 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሊያስብል በሚችል ሁኔታ ሐዘናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ በአፍሪካና በዓለም ላይ ያሉ መሪዎችም የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሞት ተከትሎ የሐዘን መግለጫቸውን በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ቆንስላዎቻቸው አማካይነትና በተለያዩ የዜና አውታሮች እየገለጹ ይገኛሉ፡፡