ሳያርፍ ያረፈው መለስ

ባለፈው ማክሰኞ ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ ስልክ የተደወለው በጣም በጠዋት ነበር፡፡ የስልክ መልዕክቱም የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈት ሕይወት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይፋ ሊደረግ እንደሆነ የሚገልጽ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የ1፡00 ሰዓት የዜና እወጃው ላይ የዕለቱ ተረኛ ዜና አንባቢ በረጅሙ ከተነፈሰ በኋላ በርካቶችን ያስደነገጠውን፣ ያሳዘነውንና ታሪካዊ የሆነው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ዜና ዕረፍት እንባ እየተናነቀው አነበበ፡፡