ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ማረፋቸውን በመጨረሻ መንግሥት አመነ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነኀሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም. August 21, 2012)፦ በመጨረሻም የኢትዮጵያ መንግሥት ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በ57 ዓመታቸው ማረፋቸውን ዛሬ ጠዋት በመንግሥት መገናኛ ብዙኀኑ አማካኝነት አመነ። ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ላለፉት ሁለት ወራት ከመገናኛ ብዙኀን ከመጥፋታቸውም በላይ በውጭ ሀገር የሚገኙ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን መታመማቸውን ቀጥሎም ማረፋቸውን ቢዘግቡም፤ አቶ በረከት ስምዖንን ጨምሮ ሌሎች ባለሥልጣናትም አቶ መለስ በሐኪም በታዘዘ እረፍት ላይ መሆናቸውን ሲገልጹና ሲያስተባብሉ መክረማቸው ይታወሳል።