ሊቢያ፥ ከአምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ

ከአርባ ዓመታት በላይ በአንድ ግለሰብ አምባገነናዊ አገዛዝ ስር የቆዩት ሊቢያውያን በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ሽግግር ላይ ይገኛሉ። በነፃ ሂደትም የምክር ቤቱን ፕሬዚዳንት ሾሞዋል። በቅርቡ ዲሞክራሲያዊ ሕገ-መንግስት ተረቆ ሂደቱ እንደሚፋጠን የመነገሩን ያህል፤ ሊቢያን የፀጥታ እና የእስላም አክራሪነት ችግርም ያሰጋታል እየተባለ ነው።