አትሌት መሰረት ደፋር ለኢትዮጵያ ሦስተኛውን ወርቅ አስገባች
ጥሩነሽ ዲባባ ደግሞ ነኀስ

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 4 ቀን 2004 ዓ.ም. August 10, 2012)፦ አትሌት መሰረት ደፋር ዛሬ ማምሻውን በለንደን ኦሎምፒክ በተካሄደው የአምስት ሺህ ሜትር የሴቶች ሩጫ ውድድሩን በአንደኝነት በመጨረስ የወርቅ ሜዳሊያ ስታገኝ ጥሩነሽ ዲባባ ደግሞ ሦስተኛ በመውጣት የነኀስ ሜዳሊያ አግኝታለች። ገለታ ቡርቃ ደግሞ አምስተኛ ሆናለች።