የአንድነት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አመራሮች ፍርድ ቤት ቀርበው በግሳጼ ታለፉ

በእነ አንዱዓለም አራጌ ላይ ፍርድ ቤት የሰጠውን የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔን በመቃወም ‹‹ፍርድ ቤቱን ደፍረዋል›› በሚል ከትናንት በስቲያ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው የነበሩት፣ የአንድነት ለፍትሕና ዲሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) አመራሮች በማስጠንቀቂያና በግሳጼ ታለፉ፡፡