ኢትዮጵያዉያን ተፈናቃዮች በደቡብ

ደቡብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በጎሳ መካከል የተነሳ ግጭት ከሃያ በላይ ሰዎችን ህይወት አሳጥቶ በርካቶችን ለጉዳት ዳርጎ፤ ሺዎችን ወደጎረቤት ኬንያ ካሰደደ ቀናት ተቆጥረዋል። የኬንያ ቀይ መስቀል ከ10 እስከ 15 ሺህ የሚገምታቸዉ ኢትዮጵያዉያን ተሰዳጆችን የሚረዳበት ድጋፍ ባስቸኳይ እንዲቀርብለት አመልክቷል።