ከገምሻት ተራራ ስር

ሰሜን ወሎ ኡርጌሳ የሚባል ቦታ ላይ ነው የሚገኘው፤ ገምሻት አማተር ከያኒያን የስነፅሁፍ ክበብ ይሰኛል። የክበቡ አባላት የዛሬ ሶስት ዓመት ግድም መስከረም ወር ላይ ጥቂት ሆነው ሲሰባሰቡ ያለማንም አደራጅነት በራሳቸው ተነሳሽነት ነበር። ዛሬ ክበቡ 22 ወንዶችን እና 8 ሴቶችን ያካተተ የወጣት ስብስብ አባላት አሉት።