የአፍሪቃና የአሜሪካ ንግድ

የአፍሪቃ የጨርቃ-ጨርቅ ፋብሪካዎች ለአሜሪካ ታላላቅ መደብሮችና ባለሞዶች አልባሳትንና ሌሎች ምርቶችን ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ይህ ሊሆን የቻለው ደግሞ በአሕጽሮት አጎአ ተብሎ በሚጠራው በአሜሪካ መንግሥት «ግሮውዝ ኤንድ ኦፖርቹኒቲ አክት» የዕድገትና የዕድል ሕግ» አማካይነት ነው።