የኢሳት መንፈስና የኢሳት ሸክም

የኔታ ተክሌ – (ቶሮንቶ-ካናዳ)

ከዲሲ ማርያም እስከ ቶሮንቶ ማርያም

በሳን ሆሴ (ዜ) ያየሁትም በዚያ በኮለምበስ እንዳየሁት ነው። በኮምበስ ያዩሀት በአትላንታ እንደመሰከርኩት እንደሆነው ማለቴ ነው። በርግጥ በነዚህ ከተሞች ያየሁት በቶሮንቶ ወይንም በዲሲ ቅድስት ማሪያም እንዳየሁት አይሆንም። የዛሬ ወር ከግማሽ አካባቢ ነው፤ ባንድ እለተ-ሰንበት፤ በዲሲ ቅድስት ማሪያም ከረፈደ ተገኝቼ፤ ያው ከረጅሙ የኛ ቤተክርስቲያን አገልግሎት በሁዋላ፤ ቄሱ በዚያ ሳምንት ለህንጻ ማሰሪያ የተዋጣውን ገንዘብ መዘርዘር ጀመሩ። አንዳንድ ግዜ የመዋጮውን ብዛት ሳስበው፤ የዛሬ አራት ወር የሰማሁትን እየደገሙት ነው ወይስ አዳዲስ መባእ ነው ያስብለናል።