የአሸባብ ጥቃት ዒላማ ኬንያ

ኬንያ ባለፈው እሁድ ከተጣለው ጥቃት ጋ ግንኙነት አላቸው ያለቻቸውን አራት ተጠርጣሪዎችን ማሰርዋን አስታወቀች። በወደብ ከተማ ሞምባሳ ከትናንት በስቲያ ማታ በተጣለ የእጅ ቦምብ የሦስት ሰዎች ሕይወት ሲጠፋ፣ ሀያ አምስትም ቆስለዋል።