አየር መንገድ ያባረራቸውን ቴክኒሻኖች ወደ ሥራ መለሰ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦይንግ 777 የመንገደኞች አውሮፕላን ላይ ጉዳት በማድረስ አራት ሚሊዮን ብር አክስረውኛል በማለት ከሥራ አባሯቸው የነበሩትን ሁለት ከፍተኛ ቴክኒሻኖች ወደ ሥራ እንዲመለሱ ወሰነ፡፡ ሠራተኞቹ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ሥራ የተመለሱ መሆናቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡