የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሠራተኛ በፖሊሶች ተደብድቦ መሞቱ ተገለጸ
– ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ውለዋል
ላለፉት አምስት ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መሥሪያ ቤት በተለያዩ የሥራ ክፍሎች ይሠራ የነበረው አቶ ሀሚድ ወዳጆ የተባለ ግለሰብ፣ ሰኔ 2 ቀን 2004 ዓ.ም ምሽት ላይ ቄራ አካባቢ በፖሊሶች በደረሰበት ከባድ ደብደባ ሕይወቱ ማለፉን ቤተሰቦቹ ለሪፖርተር ገለጹ፡፡