ኢትዮጵያውያን በዚህች ሰዓት (ተሻለ መንግሥቱ)

ተሻለ መንግሥቱ

በውጪ ሀገራት የምትኖሩ ወገኖቻችን እኛ በሀገር ውስጥ ያለነው ወገኖቻችሁ እየኖርን እሚመስላችሁ ከሆነ እያልኖርን መሆናችንን ትረዱ ዘንድ ይህችን አጭር ዘገባ በጥሞና አንብቡና የምንገኝበትን ሰቆቃ ተገንዘቡልን፤ ‹እኛ› ስል ብዙዎቻችንን ማለቴ እንጂ የኀልውናችን መረጋገጥ ለኅልውናቸው ማሸብረቅ መሠረት የሆነውን እነአያ እንደልቡን እንዳልሆነ መቼም ካለተጨማሪ ማብራሪያ ይገባችኋል ብዬ እገምታለሁ።