የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዓመታዊ ዘገባ

የፖለቲካ ለውጥ ለማስገኘት ሲባል አደባባይ መውጣት ድፍረትን ይጠይቃል። በሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪቃውያንም ይህ ድፍረት እንዳላቸው ባለፈው ዓመት አስመስክረዋል። በሰሜን አፍሪቃ እና በመካከለኛው ምሥራቅ ብቻ ሳይሆን ፡ ከሰሀራ በስተደቡብ ባሉት አፍሪቃውያት ሀገሮችም እጅግ ብዙ ሕዝብ በሰብዓዊ መብት ጥሰት አንጻር አደባባይ በመውጣት ተቃውሞ አሰምቶዋል።