የድርጊት መርሐ ግብሩ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት አፈጻጸም ይለውጠዋልን?

ባለፈው ሳምንት ግንቦት 6 እና 7 በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለተሰብሳቢዎቹ ይፋ የተደረገው የብሔራዊ የሰብዓዊ መብቶች የድርጊት መርሐ ግብር ረቂቅ ሰነድ በመንግሥት ፀድቆ ወደ ሥራ ለመግባት እንዲቻል ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡