በብራስልስ የአውሮፓ ኮሚሽን የተቃውሞ ሰልፍ ተጠራ
-
የኢትዮጵያ መንግሥት በዜጎቹ ላይ እያደረሰ ያለውን የመብት ረገጣ እና እስራት በአስቸኳይ ያቁም!!
-
በኃይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባቱን እና ዜጎችን ማፈናቀሉን ያቁም!!
Ethiopia Zare (ሐሙስ ግንቦት 2 ቀን 2004 ዓ.ም. May 10, 2012)፦”መብታችን ይከበር!” በሚል በኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተጀመረውን እንቅስቃሴ በመደገፍና ”የኢህአዴግ መንግሥት በዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን የመብት ረገጣ፣ እስራት፣ በኃይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባቱንና ዜጎችን ማፈናቀሉን ያቁም!” በሚል መሪ መፈክር የፊታችን ሜይ 16 ቀን 2012 በብራስልስ የአውሮፓ ኮሚሽን ሕንፃ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ ተጠራ።