የተበላሹ ምግቦችና መድሃኒቶች በኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ ነዎት? ለመመኘቱ አያድርስብዎት እንበል። ግን ያዉ ሰዉ ነዎትና ታመሙ እንበል። ሐኪምዎ የሰጠዎትን የመድሐኒት ማዘዢያ ይዘዉ መድሐት መደብር ሲሄዱ፥ አንድ አስተያየት ሰጪ እንደነገሩን፥ አስተናጋጅዎ የየትኛዉን ሐገር ይፈለጋሉ? የጀርመን፥ የሕንድ፣ የቻይና… እያለ ይጠቅዎታል። ለነገሩ መድሐኒት መደብር መሔድም አያስፈልግዎ — ካንዱ ሱቅ በደረቴ ኪንን መሸመትም ይችላሉ። ኪኒኑ አዳኝዎ – ይሁን ገዳይዎ የሚያዉቁት ግን ከወሰዱት በሕዋላ ነዉ። ቀደም ሲል ቅቤ ፈልጎ ልቁጥ ሙዝ ፥ በርበሬ አገኘሁ ብሎ የተፈጨ ሸክላ ገዛሁ ባይ ምሬት ነበር የሚሰማዉ። አሁን ደግሞ የድሬዳዋዉ ወኪላችን ዩሐንስ ገብረ እግዚአብሔር እንደዘገበዉ፥ የአገልግሎት ጊዜዉ ያለፈበት፥ ወይም ጊዜዉ የተሰረዘ፥ በጥንቃቄ ያልተያዘ፥ ምግብና መድሐኒት በየመደብሩ፥ በየጎዳናዉ ይቸበቸባል አሉ። ያዳምጡ
[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/41F3391B_1_dwdownload.mp3[/podcast]