ሚስቱን በአሲድ አቃጥሎ ደቡብ ሱዳን ተደብቆ የተያዘው በሞት እንዲቀጣ ተጠየቀ

ባለፈው ዓመት ሚያዝያ 30 ቀን 2004 ዓ.ም በልጁ እናት ላይ አንድ ሊትር ሰልፈሪክ አሲድ ደፍቶ ከተሰወረ በኋላ፣ ደቡብ ሱዳን ውስጥ በቁጥጥር ሥር የዋለው ግለሰብና ሁለት ግብረ አበሮቹ በሞት እንዲቀጡ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በትናንትናው ዕለት ጠየቀ፡፡ አሲዱ የተደፋባት ግለሰብ በሁለተኛው ቀን መሞቷ ይታወሳል፡፡