የብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ሥርዓተ ቀብር ቅዳሜ ይፈጸማል


ደጀ ሰላም፤ ማርች 4/2011)፦ ሐሙስ የካቲት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት የብፁዕ አቡነ ይስሐቅ፣ የባሌ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሥርዓተ ቀብር ነገ ቅዳሜ በአዲስ አበባው የመንበረ ፀባዖት ቅ/ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀም ታውቋል። ዛሬ አርብ አስከሬናቸው ካረፈበት ከባልቻ ሆስፒታል ወደ ካቴድራሉ የተዘዋወረ ሲሆን ሌሊቱን ጸሎተ ፍትሐት እንደሚደረግላቸው ምንጮቻችን በተለይ ለደጀ ሰላም ገልጸዋል።

(Read More ወደሚቀጥለው ገጽ ይዞራል . . . . .)