የሕገወጥ የጫት ነጋዴዎች ክስ በአሜሪካ ፍርድቤት

አሥራ ሶስት የሶማልያና የየመን ተወላጅ የሆኑ አሜሪካውያን ጫትን በህገወጥ መንገድ ወደ ዩኤስ አሜሪካ አስገብተዋል በሚል በሀገሪቱ ፌዴራዊ ፍርድ ቤት ክስ ተመሰረተባቸው። ተከሳሾቹ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብዙ ሚልዮን የሚቆጠር ዶላር ያስገኘ ጫት ማዛዋወራቸውን የክሱ መዝገብ አመልክቶዋል። የህግ ባለሞያና ጠበቃዉ ዶክተር ፍፁም አቻሜለህ ፊደራሉ ህግ ላይ በወንጀልነት የተጠቀሰዉ ይላሉ « በፊደራሉ ህግ የተፃፈዉ ጫት ዉስጥ ስላሉ ንጥረ ነገሮች ነዉ። አንደኛዉ ካቲኖን የተባለ ንጥረ ነገር ሲሆን ፣ ሁለተኛዉ ደግሞ ካቲን የተባለ ንጥረ ነገር ነዉ ያለዉ ጫት። ካቲኖን የሚገኘዉ ጫት ከተቆረጠ 48 ሰዓት ያልሞላዉ እርጥብ ጫት ዉስጥ ነዉ። በአሜሪካ ዉስጥ እርጥብ ጫት ይዞ መገኘት ከአንድ ዓመት በላይ የሚያስቀጣ ከባድ ወንጀል ነዉ።»

[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/AE9ECD3D_1_dwdownload.mp3[/podcast]