የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስለ አለም ደቻሳ ያቀረበዉ ጥያቄ
የመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ መብት ጉባኤ የዘመናዊ ባርነት ክፍል በሊባኖስ የኢትዮጵያዊትዋን የአለም ደቻሳን አሟሟት በተመለከተ የሊባኖስ መንግስት መርምሮ ይፋ እንዲያደርግ ጠየቀ። ተቋሙ በሊባኖስ ዉስጥ የሚኖሩ ከ 200,000 በላይ የዉጭ አገር ዜጎች በግርድና እየሰሩሩ መሆኑን ገልጾ፣ ከፍተኛ እንግልት እና ስቃይ እንደሚደርስባቸዉ አስታዉቆአል። የ33 አመትዋ ኢትዮጵያዊት አለም ደቻሳ፣ በአሰሪዎችዋ ከተደበደበች በኋላ እራስዋን ማጥፋትዋ የሚታወስ ነዉ። ይህንኑ የአለም ደቻሳን ሞት ተከትሎ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ እና የኢትዮጵያዉያን እና የዉጭ ተቋማት ተቋማቸዉን በተደጋጋሚ ሲያሰሙ ቆይተዋል።
[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/6AF70C7F_2_dwdownload.mp3[/podcast]